አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ አሸባሪው ትህነግ በአማራ ክልል በፈጸመው ወረራ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

229
ደሴ: መስከረም 06/2014 ዓ.ም (አሚኮ) አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ
ከሰሜን ወሎ ዞን ተፈናቅለው ኮምቦልቻ ከተማ ለተጠለሉ ወገኖች ነው ድጋፉን ያደረገው።
ለተፈናቃዮቹም 500 ኩንታል ዱቄት እና 2 ሺህ 500 ሊትር ዘይት ድጋፍ አድርጓል። ድጋፉም 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር እንደሚያወጣ ተገልጿል።
ድጋፉም በኃይሌ እና ዓለም ኢንተርናሽናል ኀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ስም የተደረገ ነው ተብሏል።
አትሌቱ በአፋር ክልል በአሸባሪው የትህነግ ቡድን ወረራ ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ዜጎች ድጋፍ እንደሚያደርግም አስታውቋል።
ዘጋቢ:- ከድር አሊ – ኮምቦልቻ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleየዓለም የምግብና የእርሻ ድርጅት (FAO) ልዑክ በአማራ ክልል ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረስ ከርእሰ መሥተዳድር አገኘሁ ተሻገር ጋር እየተወያየ ነው።
Next articleየመገናኛ ብዙኃን የሥራ ኀላፊዎች አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን በደቡብ ጎንደር ዞን ያደረሰውን ጉዳት እየተመለከቱ ነው።