በሰልፎቹ የተሳተፉ የእስልምና ሀይማኖት ተከታዮች በቤተ ክርስቲያኗ እና በምዕመኖቿ ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት አወገዙ፡፡

337

ባሕር ዳር፡ መስከረም 18/2012 ዓ/ም (አብመድ) ዛሬ በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሀይማኖት ተከታዮች በቤተ ክርስቲያኗ እና በምዕመኖቿ ላይ እየተፈጸመ ያለውን ጥቃት በማውገዝ ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል፡፡

በቤተ ክርስቲያኗ እና በምዕመኖቿ ላይ ጥቃት የፈጸሙ አካላት በህግ እንዲጠየቁም ነው በሰልፎቹ የጠየቁት፡፡ በሰላማዊ ሰልፎቹ የእስልምና ሀይማኖት ተከታዮችም ተሳትፈዋል፤ በቤተ ክርስቲያኗ እና በምዕመኖቿ ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃትም አውግዘዋል፡፡

ዛሬ ሰልፍ ከተካሄደባቸው ከተሞች መካከል የሽንዲ፣ የአጅባር እና የሰቆጣ ከተሞች የእስልምና ሀይማኖት ተከታዮች ናቸው በሰልፎቹ በመገኘት ለኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስትና ሀይማኖት ተከታዮች ያላቸውን አጋርነት የገለጹት፡፡

Previous articleሰላማዊ ሰልፎቹ በሰላም ተጠናቅቀዋል፡፡
Next article“ ግፋታ” የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ በዓል እየተከበረ ነው፡፡