የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ለተፈናቃዮች 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር የሚገመት የምግብ እና አልባሳት ድጋፍ አደረገ፡፡

237
ደሴ፡ ጳጉሜን 02/2013 ዓ.ም (አሚኮ) ሽብርተኛው የትህግ ወራሪ ቡድን በፈጸመው ጥቃት ከተለያየ አካባቢ ተፈናቅለው በደሴ ከተማ ተጠልለዉ ለሚገኙ ተፈናቃዮች የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ሠራተኞችና የሥራ ኀላፊዎች የምግብ እና አልባሳት ድጋፍ አድርገዋል፡፡
ድጋፋን በደሴ ከተማ ተገኝተዉ ያስረከቡት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቤል አዳሙ ተቋሙ በአፋር እና በአማራ ክልሎች በሽብርተኛው ትህነግ ወረራ ምክንያት ለተፈናቀሉ ዜጎች ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጭ ድጋፍ ማድረጋቸዉን አንስተዋል፡፡
ኮርፖሬሽኑ ተፈናቃዮችን በዘላቂነት ለማቋቋምም ያላሰለሰ ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል፡፡
ድጋፉን የተረከቡት የደሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አበበ ገብረመስቀል ለተደረገዉ ድጋፍ ምሥጋና አቅርበው በተባበረ ክንድ ይህንን ቀን ማለፍ ይገባል በማለት ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ማኅሌት ተፈራ-ከደሴ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleበ34ኛ ዙር የብርሸለቆ መሰረታዊ ወታደሮች ምረቃ ላይ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን እና ልዑካቸው ተገኝተዋል፡፡
Next article“የዛሬ ተመራቂዎች ሽብርተኛው ትህነግን ለመፋለም በሕዝብ የተሸኛችሁ የቁርጥ ቀን ልጆች መሆናችሁ ልዩ ያደርገዋል” ኮሎኔል ጌታቸው አሊ የብር ሸለቆ መሠረታዊ ውትድርና ማሠልጠኛ ትምህርት ቤት ዋና አዛዥ