የመስቀል ደመራ በዓል ያለምንም የፀጥታ ችግር መከበሩን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

233

ባሕር ዳር፡ መስከረም 17/2012 ዓ/ም (አብመድ) በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የመስቀል ደመራ በዓል ከትናንት ጀምሮ ተከብሯል። የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የሚድያ አስተባባሪ ምክትል ኮማንደር መሠረት ላቀ ለአብመድ እንደተናገሩት በዓሉ በሠላም ሊጠናቀቅ የቻለው የሃይማኖቱ ተከታዮች፣ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶችና የክልሉ የፀጥታ ኃይሎች በጋራ ባደረጉት አስተዋጽኦ ነው።

በተለይ በአብዛኛዎቹ የክልሉ አካባቢዎች የሚገኙ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ከትናንት ጀምሮ በዓሉ በሠላም እንዲጠናቀቅ ጉልህ ድርሻ እንደነበራቸው ነው ምክትል ኮማንደሩ የገለጹት። ወጣቶቹ ከፀጥታ ኃይሎች ጎን በመሆን ሠላማዊ እንቅስቃሴ እንዲኖርና ወንጀል እንዳይፈጠር በማስተባበር ላሳዩት መልካም ተግባርም ምሥጋና አስተላልፈዋል።

ዘጋቢ:- ኃይሉ ማሞ

Previous articleየመስቀል ደመራ በዓል በካርቱም መድኃኒዓለም ተከብሯል፡፡
Next article‹‹የአማራን ክልል የጦርነት አውድማ ለማድረግ የሚጥሩ አካላት አይሳካላቸውም፤ ይህን ለማድረግ የሚመጡ ካሉም ለመከላከል አቅሙ፣ ብቃቱም አለን፡፡›› አቶ አገኘሁ ተሻገር