አሸባሪው የትህነግ ቡድን በወሎ ግንባር ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ እየደረሰበት ነው” ብርጋዴር ጀኔራል ሻምበል ፈረደ

553

ደሴ፡ ነሐሴ 30/2013 ዓ.ም (አሚኮ) ከወሎ ግንባር አዛዦች መካከል አንዱ የሆኑት ብርጋዴር ጀኔራል ሻምበል ፈረደ አሸባሪውና ወራሪው የትህነግ ቡድን እየተመታ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ እየደረሰበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

አሸባሪ ቡድኑ ከፍተኛ የሰው ኀይል አሰልፎ ወደ ወረባቦና ተሁለደሬ ወረዳዎች ሰርጎ ለመግባት ቢመጣም የጀግናውን የመከላከያ ሠራዊት ጠንካራ ምት መቋቋም አቅቶት ሙትና ቁስለኛ እየሆነ ነው ቀሪውም እየተመለሰ ነው ብለዋል፡፡

የመከላከያ ሠራዊቱ ሀገር ለማፍረስ አስቦ የመጣውን አሸባሪ ቡድን ለመደምሰስ በከፍተኛ ወኔ እየተፋለመ መሆኑን ገልጸው የሕዝቡ ደጀንነት ከፍተኛ እንደሆነም ብርጋዴር ጀኔራል ሻምበል ፈረደ ተናግረዋል፡፡

አሁን ላይ የቡድኑ አባላት እየተደመሰሱ ነው፤ በቀጣይም በቡድኑ ላይ የሚወሰደው ርምጃ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

ዘጋቢ፡- ተመስገን አሰፋ – ከወሎ ግንባር

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

Previous articleየጎንደር ዩኒቨርሲቲ ምሁራን መማክርት በሀገር ውስጥና በኩዬት የሚኖሩ አማራዎችን በማስተባበር በማይጠብሪ ግንባር ጠላትን እየደመሰሰ ለሚገኘው የወገን ጦር ድጋፍ አደረጉ፡፡
Next articleየገቢዎች ሚኒስቴር፣ ጉምሩክ ኮሚሽን እና ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ከ71 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ለተፈናቀሉ ወገኖች እና አሸባሪውን የትህነግ ቡድን እየተፋለሙ ላሉ የጸጥታ አካላት ድጋፍ አደረጉ፡፡