አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ በሱዳን ከቱርክ አምባሳደር ጋር በሁለትዮሽና ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አደረጉ።

222

ባሕር ዳር፡ ነሐሴ 25/2013 ዓ.ም (አሚኮ) በሱዳን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ በሱዳን ከቱርክ አምባሳደር ኢርፋን ናዚር ኦግሉ ጋር በሁለትዮሽና ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።

በውይይቱም ሁለቱ አምባሳደሮች በኢትዮጵያና ቱርክ መካከል ያለውን ጠንካራ ወዳጅነት እና ስትራቴጂካዊ ግንኙነት በተመለከተ ሀሳብ ተለዋውጠዋል።

በተጨማሪም፣ አምባሳደር ይበልጣል በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ዙሪያ፣ በኢትዮጵያና ሱዳን መካከል ያለውን የድንበር ሁኔታ እንዲሁም የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በተመለከተ ስላለው አሁናዊ ሁኔታ ማብራሪያ መስጠታቸውን በሱዳን የኢትዮጵያ ኢምባሲ አስታውቋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

Previous articleየምዕራብ ጎጃም ዞን ሕዝብ ለወገን ጦርና በአሸባሪው ትህነግ ወረራ ለተጎዱ ዜጎች ድጋፍ አደረገ።
Next article“የጠቅላይ ሚኒስትሩ የኡጋንዳና ሩዋንዳ ጉብኝት ውጤታማ ነበር” የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር