በማይጠብሪ ግንባር በደባርቅ ወረዳ በጫንቅና በዳባት ወረዳ ጭና ቆርጦ ለመግባት የሞከረው አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን ተደመሰሰ።

432

ባሕር ዳር፡ ነሐሴ 25/2013 ዓ.ም (አሚኮ) ዛሬ ጥዋት በደባርቅ ከተማ በጫንቅና በዳባት ወረዳ ጭና ቆርጦ ለመግባት የሞከረው አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን በመከላከያ ሠራዊት፣ በልዩ ኃይል፣ በሚሊሻና ፋኖ ከባድ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ እንደደረሰበት የዳባት ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ሰውነት ውባለም ለአሚኮ ገልጸዋል።

ወራሪው ቡድን ያሰበው እንዳልተሳካለት ተናግረዋል።
ከዚህ በፊት ሕዝቡን በማንቃት የተሠራው ሥራም ውጤት አስመዝግቧል ነው ያሉት።

የገባበት አካባቢም እሾህ ሆኖ ጠብቆታል ብለዋል፤ አጅሬ ጃኖራን ቆርጦ ለመሄድ ቢያስብም ተደምስሶ መቅረቱን ተናግረዋል።

ዓላማው በአካባቢ ሽብር ፈጥሮ ከግብፅ ተላላኪዎች ለመገናኘት ነበር፤ የጸጥታው ኀይል ከአራት ቀን በላይ ውጊያ አድርጓል፤ በተሠራው ጠንካራ ሥራም ማለፍ አልቻለም ብለዋል ዋና አስተዳዳሪው። ቆርጦ በመግባት ደባርቅንና ዳባትን ለማለያየት ያሰበው ዓላማም ከሽፏል ነው ያሉት።

ዘጋቢ፦ አዳሙ ሽባባው- ከማይጠብሪ ግንባር

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

Previous articleዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ሚዛናዊ እይታ እንዲኖራቸው የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አገኘሁ ተሻገር ጠየቁ፡፡
Next article“ሽብርተኛው ትህነግ ደሴ ከተማ ገብቶ እንዲዘርፍ እና የአማራነት ክብራችንን እንዲነካ አንፈቅድም” የደሴ ከተማ አስተዳደር ነጋዴዎች