ወራሪው እና አሸባሪው የትህነግ ቡድን በሀራ ገበያ ከተማ አስተዳደር ያደረሰው ጥፋት ለሕዝብ ያለውን ጥላቻ እንደሚያሳይ የከተማዋ ከንቲባ ገለጹ፡፡

440
ባሕር ዳር: ነሐሴ 23/2013 ዓ.ም (አሚኮ) ወራሪው እና አሸባሪው የትህነግ ቡድን ወረራ በፈጸመበት የሀራ ገበያ ከተማ አስተዳደር የንጹሐንን ሕይወት ቀጥፏል፤ ንብረት አውድሟል፤ ዝርፊያ ፈጽሟል፡፡
ከከተማ አስተዳደሩ 15 ኪሎ ሜትር ገደማ ርቀት የሀብሩ ወረዳ ቁጥር 24 ቀበሌ ነዋሪ ታሪክ የማይረሳው ጀብድ ፈጽሟል፡፡
የሀራ ገበያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መሐመድ አዲስ እንዳሉት ወራሪው እና አሸባሪው የትህነግ ቡድን በከተማ አስተዳደሩ የፈጸመው ጥፋት ቡድኑ በሕዝብ ላይ ያለውን ጥላቻ ማሳያ ነው፡፡ የሕዝብ መገልገያ ተቋማት ከጥቅም ውጭ ሆነዋል፤ የግለሰቦች ንብረት ወድሟል ፤ ተዘርፏል ብለዋል፡፡ እናም ይህን አውዳሚ የሀገር እና የሕዝብ ጠላት በጋራ መደምሰስ ይገባል ነው ያሉት፡፡
ወራሪው እና አሸባሪው የትህነግ ቡድን በሚያሰራጨው የሐሰት ወሬ ሕዝቡ ሳይረበሽ አካባቢውን ሊጠብቅ ይገባል ብለዋል፡፡
የሀብሩ ወረዳ ቁጥር 24 ቀበሌ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን ከአሸባሪ ቡድኑ ወራሪና ሰርጎገብ እየጠበቁ ይገኛሉ ነው ያሉት። ነዋሪዎቹ ከመከላከያ ሠራዊት፣ ከልዩ ኀይል ፣ ሚሊሻ እና ፋኖ ጋር የሽብር ቡድኑን እየተፋለሙ መሆኑንም ለአብነት አንስተዋል፡፡
ወራሪው እና አሸባሪው የትህነግ ቡድንን ለሚፋለሙ የጸጥታ አካላት አስተማማኝ ደጀን በመሆን ቡድኑን በአጭር ጊዜ መደምሰስ እንደሚገባ ከንቲባው ተናግረዋል፡፡
ለነዋሪዎች የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ እንዲቀርብ ሁሉም እንዲረባረብም አቶ መሐመድ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ዘጋቢ፡- የማነብርሃን ጌታቸው
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleአሸባሪው እና ወራሪው የትህነግ ቡድን ከእያንዳንዱ የቤተሰብ አባላት ወደ ጦርነት በግዴታ እንዲገቡ እያደረገ እንደሚገኝ በማይጠብሪ ግንባር እጃቸውን የሰጡ የቡድኑ አባላት ገለጹ፡፡
Next articleአሸባሪውንና ወራሪውን የትህነግ ቡድን ለመደምሰስ በሚደረገው ትግል ወጣቶች ከፍተኛ ጀብዱ እየፈጸሙ መሆኑን የሰሜን ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ገለጹ፡፡