በውስጥ ሱሪው ደብቆ 12 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ከሀገር ሊያስወጣ የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

372

ባሕር ዳር፡ መስከረም 17/2012 ዓ/ም (አብመድ) በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የጂግጂጋ ቅርኝጫፍ ጽሕፈት ቤት የቶጎ ጫሌ መቅረጫ ጣቢያ በሕገ ወጥ መንገድ ከሀገር ሊወጣ የነበረ 12 ሺህ የአሜሪካ ዶላር መያዙ ተነግሯል፡፡

በፍተሻ እጅ ከፍንጅ እንደተያዘ የተገለጸው ግለሰብ በሕገ ወጥ የገንዘብ ዝውውሩ የሚያገኘውን ብር የሚያከማችበት የሦስት የተለያዩ ባንኮች ደብተሮች እንደተገኙበትም የገቢዎች ሚኒስቴር ያወጣው መረጃ ያመለክታል፡፡

Previous article“ንጉሥ ዳዊት በፍቅር የተቀበለውን መስቀል ወደ ሀገሩ በክብር ማድረስ ባይችልም፤ አባት የጀመረውን ልጅ ይጨርሳልና ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ መስቀሉን ይዞ ሀገሩ ገብቷል፡፡”
Next article“ዮ መስቀላ” የጋሞዎቹ የዘመን መለወጫ::