“የአማራን ሕዝብ ለመውረር በሀገር አጥፊው ኀይል አማካኝነት በውዴታም ሆነ በግዴታ ወደ አማራ መሬት የገባችሁ ሁሉ እጃችሁን ለመከላከያና ለአማራ ልዩ ኀይል እንድትሰጡ እናሳስባለን” አቶ ቀለመወርቅ ምህረቴ

281
የደቡብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ ቀለመወርቅ ምህረቴ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የሰጡት ማሳሰቢያ ቀጥሎ ቀርቧል።
የአማራን ሕዝብ ለመውረር በሀገር አጥፊው ኀይል አማካኝነት በውዴታም ሆነ በግዴታ ወደ አማራ መሬት የገባችሁ ሁሉ እጃችሁን ለመከላከያና ለአማራ ልዩ ኀይል እንድትሰጡ እናሳስባለን።
እጁን በሰላም ለሚሰጥ ተዋጊ ኀይል በዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ ሕግ መሰረት ምህረት የሚደረግለት እና ደኅንነቱ የሚጠበቅለት መሆኑን እንገልጻለን።
እጅ ለሚሰጡ ኀይሎች የአጭር ጊዜ ስልጠና በመስጠት ወደ ሚፈልጉት ቦታ በአግባቡ የምንሸኝ ይሆናል።
Previous articleበዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው የሚገኙ ታዳጊ ኢትዮጵያውያን የቡሄ በዓልን በማስመልከት ለታላቁ ህዳሴ ግድብ የገቢ ማሰባሰቢያ መርኃግብር አካሄዱ።
Next article“አይሻገሩም፤ ከተሻገሩ ደግሞ አፈር ለማልበስ አንሳሳም” የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዋና አስተዳዳሪ