
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በማኅበራዊ የትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ እንዳሉት “ኢትዮጵያን ለማዳን እዘምታለሁ መቼም፣ የትም፣ በምንም” በሚል መሪ ቃል፣ የብሔራዊ ቴአትር፣ የኦሮሞ የባህል ማዕከልና የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች የኪነ ጥበብ ባለሞያዎች በወታደራዊ ማሠልጠኛዎች ተገኝተው ዝግጅቶችን አቅርበዋል።
“ኪነ ጥበብ ምንጊዜም ከኢትዮጵያ ጀግንነት ጋር ናት። ዝግጅቶቹን ላቀረቡ የኪነ ጥበብ ባለሞያዎች ምስጋናዬን አቀርባለሁ። ሌሎችም ከያንያን አርአያነታችሁን እንደሚከተሉ ተስፋ አደርጋለሁ” ብለዋል፡፡