የወሎ ላልይበላ የባሕል ቡድን በግንባር ተገኝቶ ለሠራዊቱ የማነቃቂያ ዝግጅት እያቀረበ ነው።

207
ባሕር ዳር፡ ነሐሴ 10/2013 ዓ.ም (አሚኮ)የኪነጥበብ ባለሙያዎች ለሀገር መከታ የሆነው ሠራዊት እያበረታቱ መሆናቸውን ስንዘግብ መቆዬታችን ይታወሳል። ዛሬ ደግሞ የወሎ ላልይበላ የባሕል ቡድን በወሎ ግንባር ሠራዊቱን እያበረታታ ነው። ከወሎ ላልይበላ የኪነት ቡድን በተጨማሪ ካቤናት ኢትዮጵያ እና ውብ ኢትዮጵያ መልቲ ሚዲያዎች ከአዲስ አበባ በጎ ፈቃደኛ ድምፃዊያንንና የውዝዋዜ ባለሙያዎችን አስመጥተዋል።
ድምፃዊያኑና ተወዛዋዦችም ሠራዊቱን እያበረታቱ ነው።
የኪነ ጥበብ ባለሙያዎቹ ሠራዊቱ የመጨረሻውን ድል እስኪያጣጥም ድረስ ከጎኑ እንደማይለዩም አረጋግጠዋል።
ጉዳዩ የሀገር ጉዳይ ነው፣ ሁሉም የኪነጥበብ ባለሙያ ሠራዊቱን ሊያበረታታ ይገባል ነው ያሉት።
ዘጋቢ:- ታርቆ ክንዴ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous article“ከግንባር ጠላት ሸሽቶ ሲወጣ ከቦ በመደምሰስ አንድም ጠላት እና በጠላት እጅ ያለ ንብረትና ትጥቅ እንዳይወጣ በማድረግ ማርከህ ያገኘኸውን ትጥቅ ለሰራኸው ጀብዱና ጀግንነት ሽልማት ይሁንህ” አቶ ቀለመወርቅ ምህረቴ
Next articleበአሸባሪው የሕወሓት ቡድን ላይ የማያዳግም እርምጃ እየተወሰደበት እንደሚገኝ የአፋር ልዩ ኀይል ገለጸ፡፡