ሕዝቡ አሸባሪው ትህነግን እሾህ ሆኖ እየወጋው እንደሚገኝ የደቡብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቀለምወርቅ ምህረቴ ገለጹ፡፡

648
ባሕር ዳር፡ ነሐሴ 07/2013 ዓ.ም (አሚኮ) የደቡብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቀለም ወርቅ አሸባሪው ትህነግ ወረራ በፈጸመባቸው አካባቢዎች የእምነት ቦታዎችን፣ ተቋማትን እና የግለሰብ መኖሪያ ቤቶችን እንዳወደመ ገልጸዋል፡፡ አሸባሪው ቡድን ንጹሓን ዜጎችን ገሏል፤ የግለሰብም ሆነ የመንግሥት ንብረቶችን ባደራጀው ቡድን ዘርፏል ብለዋል፡፡
በዞኑ አንዳንድ አካባቢዎች በተለይም በጋይንት አካባቢ ለመግባት የሞከረው አሸባሪው ቡድን በሀገር መከላከያ፣ በልዩ ኃይል፣ በሚሊሻ እና በፋኖ ጥምረት እየተደመሰሰ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡ ነዋሪው ሕዝብም እሾህ ሆኖ እየወጋው ይገኛል ብለዋል፡፡
ሌሎች አካባቢዎችም እንደ ጋይንት እና አካባቢው ሕዝብ አሸባሪውን ትህነግ የደረሰበት ሁሉ መውጫ መግቢያ በማሳጣት መደምሰስ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ዳግማዊ ተሠራ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleከአዲስ አበባ ወደ ባሕር ዳር የሚወስደው መንገድ በመሬት መንሸራተት በመዘጋቱ የትራንስፖርት መስተጓጎል አጋጠመ፡፡
Next article“ጀግናው ጃናሞራ ለጠገበው ጥይት፣ ለራበው እንጀራ ለማጉረስ ተዘጋጅቷል” በሰሜን ጎንደር ዞን የጃናሞራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ