
የመከላከያ ሠራዊትን ለሚቀላቀሉ የሲዳማ ክልል ወጣቶች ሽኝት እየተደረገ ነው፡፡
ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 23/2013 ዓ.ም (አሚኮ) የመከላከያ ሠራዊትን ለሚቀላቀሉ የሲዳማ ክልል ወጣቶች የሽኝት መርኃ ግብር እየተደረገ ነው፡፡
የመከላከያ ሠራዊትን በመቀላቀል የሀገሪቱን ዳር ድንበር ለማስጠበቅ ፍቃደኝነታቸውን ለገለፁ ወጣቶች ነው የሽኝት መርኃ ግብር እየተከናወነ የሚገኘው፡፡
የክልሉ መንግሥት ለመከላከያ ሠራዊት በአይነትና በገንዘብ ድጋፍ እንዳደረገ ተመልክቷል፡፡ክልሉ 50 ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጉን ከክልሉ መንግሥት ኮምዩኒኬሽን የተገኘ መረጃ ያመላክታል፡፡ በቀጣይም የሚያስፈልገውን ኹሉ ለማድረግ ክልሉ ዝግጁ መሆኑም ተገልጿል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m
