
ባሕር ዳር፡ መስከረም 14/2012 ዓ.ም (አብመድ) በጉምሩክ ኮሚሽን ጅግጅጋ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የቶጎ ጫሌ መቅርጫ ጣቢያ 7 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ 5ኪ.ግ ወርቅና የዉጪ አገር ገኝዘቦችን መያዙ ተገለጸ፡፡
የገቢዎች ሚኒስቴር በማኅበራዊ ገጹ እንዳስታወቀው በቀን መስከረም 13 ቀን 2012ዓ.ም ከሌሊቱ 9፡00 አካባቢ ለውጭ ገበያ የሚቀርብ ጫት በጫነ አይሱዚ የቶጎ ጫሌ ፈታሾች ባደረጉት ጥረትና ጠንካራ ፍተሻ 5 ኪ.ግ ጥፍጥፍ ወርቅ፣ 175 ሺህ 584 የሳውዲ ሪያል እና 7 ሺህ 155 ድርሀም በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡