የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለአርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) የክብር ዶክትሬት ሊሰጥ ነው፡፡

1030

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለአርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) የክብር ዶክትሬት ሊሰጥ ነው፡፡

ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 22/2013 ዓ.ም (አሚኮ) የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ዛሬ ባካሄደው የሴኔት ስብሰባ ነው ለአርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) የክብር ዶክትሬት ለመስጠት የወሰነው፡፡

አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ቅዳሜ ሐምሌ 24/2013 ዓ.ም በተማሪዎች ምረቃ ዕለት ተገኝቶ የክብር ዶክትሬቱን የሚቀበል ይሆናል በማለትም ዩኒቨርስቲው አስታውቋል፡፡

“ክብርህን ጠብቀህ ኢትዮጵያን ስላከበርክ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ይህን ክብር አበርክቶልሃል” በማለትም ይኒቨርስቲው ለአርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን ያለውን አድናቆት ገልጿል፡፡

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

Previous articleኅብረተሰቡ ከአሸባሪዉ የትህነግ የሀሰተኛ ፕሮፓጋንዳ በመጠንቀቅ የህልዉና ዘመቻው አካል እንዲኾን የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ጥሪ አቀረበ፡፡
Next articleየባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ መምህራን፣ ሠራተኞች እና ተማሪዎች ከ33 ሚሊዮን ብር በላይ ለህልውና ዘመቻው ድጋፍ አድርገዋል፡፡