“ትህነግን በቆፈረችው ጉድጓድ እንቀብራለን፤ ኢትዮጵያን ከጠላት ፅዱ አድርገን የጀግኖች አባቶቻችን ታሪክ እንደግማለን” የዳባት ከተማ ውትድርና ሰልጣኝ ወጣቶች

269

“ትህነግን በቆፈረችው ጉድጓድ እንቀብራለን፤ ኢትዮጵያን ከጠላት ፅዱ አድርገን የጀግኖች አባቶቻችን ታሪክ እንደግማለን” የዳባት ከተማ ውትድርና ሰልጣኝ ወጣቶች

ባሕር ዳር፡ መጋቢት 06/2013 ዓ.ም (አብመድ) በርካታ የዳባት ከተማ ወጣቶች መንግሥት ያስተላለፈውን የክተት ጥሪ ተቀብለው ጠላትን በግንባር ለመዋጋት የውትድርና ስልጠና እየወሰዱ ይገኛሉ፡፡ ከሰልጣኞቹ መካከል የዳባት ወረዳ ገንዘብና ኢኮኖሚ ግዥ ባለሙያ የሆነው ሙሳ ይርጋ “የተሰጠንን ወታደራዊ ስልጠና ተጠቅመን፣ ሴት፣ ወንድ፣ ሳንል በተባበረ ክንዳችን ሊበላን ያሰፈሰፈውን ጠላት እስከመጨረሻው ለመዋጋት ዝግጁ ነን” ብሏል፡፡May be an image of 1 person and sky

የመንግሥት ክተት ጥሪ ከተላለፈበት ዕለት ጀምሮ የዳባት ከተማ ወጣት ወደ ጦር ግንባር ሄዶ አሸባሪውን ትህነግ ለመዋጋት በአንድ ልብ ተነስቷል ያለን ደግሞ በስልጠናው ያገኘነው የዳባት ከተማ የአማራ ወጣቶች ማኅበር ሥራ አስፈፃሚ ወጣት መካሻው አምባቸው ነው፡፡ ወጣት መካሻው “ትህነግ ጦርነት የከፈተው አማራን አጥፍቶ የኢትዮጵያን ታሪክ ሊያበላሽ፣ ሕዝቦቿን ሊያዋርድ፣ ለውጭ ወራሪ አሳልፎ ሊሰጣት ነው፡፡ ይሄን እኩይ ቡድን ከቆፈረው ጉድጓድ ቀብረን ኢትዮጵያን ከጠላት ጽዱ አድርገን የአባቶቻችንን ታሪክ ለመድገም ዝግጁ ነን” ብሏል፡፡

ሌላኛዋ የዳባት ከተማ ሴቶች ሕፃናትና ወጻቶች ጽሕፈት ቤት ባለሙያ የሆነችው ቢራራ መልኬ “እስካሁን ባለው የሕግ ማስከበር ከተማ ላይ ለሠራዊቱ ካደረኩት የቀለብ ዝግጅት በተጨማሪ በጦር ግንባር ሄጄ ከፊት ለመዋጋት ወስኜ ስልጠናውን እየወሰድኩ ነው” ብላለች፡፡May be an image of 9 people, people standing and outdoors

የዳባት ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ምክትል ኮማንደር ምህረት መለሠ እንዳሉት የዳባት ከተማ ወጣት ቀድሞውንም የውትድርና ስልጠና ጥያቄ ነበረው፡፡ ጥያቄው መልስ አግኝቶ ወጣቱ ስልጠናውን እየወሰደ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ምክትል ኮማንደር ምህረት “ስልጠናው ከተደቀነብን የህልውና አደጋ ለመውጣት ጠላትን ለማጥቃትና አካባቢን በንቃት ለመጠበቅ ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል” ነው ያሉት፡፡ ስልጠናውን ሁሉም ወጣት እየተሳተፈ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ዘጋቢ፡- አድኖ ማርቆስ – ከዳባት

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
ዩቱዩብ https://bit.ly/2HYJBLZ
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

Previous articleሰዓተ ዜና ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 22/2013 ዓ.ም (አሚኮ)
Next articleአረብ ሊግ በህዳሴው ግድብ ላይ ያለውን አቋም እንደገና እንዲያየው ጥረት እንደምታደርግ አልጀሪያ አስታወቀች።