
45 ዶክተሮች እና የህክምና ባለሙያዎች ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ሙያዊ ድጋፍ ለመሰጠት ወደ ግንባር አቀኑ።
ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 20/2013 ዓ.ም (አሚኮ) በአዲስ አበባ ከተማ ካሉ ሆስፒታሎች የተውጣጡ የህክምና ባለሙያዎች የሀገር መከላከያ ሠራዊቱን ሙያዊ ድጋፍ ለማድረግ በዛሬው ዕለት በመስቀል አደባባይ አሸኛኘት ተደርጎላቸዋል፡፡
የጤና ቢሮ ኃላፊው ዶክተር ዮሐንስ ጫላን ጨምሮ 45 ዶክተሮች እና የህክምና ባለሙያዎች የሀገር መከላከያ ሠራዊቱን ሙያዊ ድጋፍ ለማድረግ ዛሬ ሽኝት የተደረገላቸው።
ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ፣ የመከላከያ ሚኒስትሩ ዶክተር ቀነአ ያደታ፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ልዩ ልዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት ለባለሙያዎቹ አሸኛኘት ተደርጓላቸዋል ።

የህክምና ባለሙያዎቹ ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት መድኃኒቶች እና የህክምና ቁሳቁስ ይዘው ተጉዘዋል።
ከዚህ ቀደም በሁለት ዙሮች ከከተማዋ የተለያዩ ሆስፒታሎች እና ጤና ጣቢያዎች የተውጣጡ ዶክተሮች እና የህክምና ባለሙያዎች ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ሙያዊ ድጋፍ ለማድረግ ወደ ትግራይ ክልል መጓዛቸውን ከአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬተሪያት ያገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ