
የጎንደር ከተማ ሚሊሻ አባላት የከተማዋን ሰላም ለማስጠበቅ እና ዘመቻ ለህልውና ለመሳተፍ ዝግጁ መሆናቸውን ገለጹ።
ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 10/2013 ዓ.ም (አሚኮ) የጎንደር ከተማ ሚሊሻ አባላት የከተማዋን ሰላም ለማስጠበቅ እና ዘመቻ ለህልውና ለመሳተፍ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የጎንደር ከተማ አስተዳደር ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ አቶ ወረታው አቡሃይ እንደተናገሩት፥ የሚሊሻ ኃይላችን የሚሰጠውን ማንኛውም ተልዕኮ ለመፈፀም ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።

ኀላፊው አክለውም ጁንታው ኢትዮጵያን ማፍረስ አንደማይችል ገልጸዋል።
የሚሊሻ አባላቱም የከተማዋን ሰላም ከማስጠበቅ ባለፈ የጁንታውን ኃይል ለመመከት ዝግጁ እንደሆኑ መግለጻቸውን ከጎንደር ከተማ ኮምዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ