
የድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ሕግን ለማስከበር ተልዕኮ ምላሽ ሰጠ፡፡
ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 09/2013 ዓ.ም (አሚኮ) የድሬዳዋ ፖሊስ ሽብርተኛው የትህነግ ቡድን ሀገርን የማፈራረስና የመበታተን የሽብር ተግባርና ተልዕኮውን ለማምከንና ሕግን ለማስከበር ለቀረበው ጥሪ ምላሽ ሰጥቷል፡፡
በዚህም መሰረት የልዩ ኃይል አባላት ወደ ግዳጅ ቀጠና እንደሚያመሩ የከተማዋ ፓሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባና የካቢኔ አባላቶቻቸው፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የኅብረተሰብ ክፍል ተወካዮች በተገኙበት ሽኝት እንደሚደረግላቸው መገለጹን ኢፕድ ዘግቧል፡፡

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ