ሁሉም የብዙኃን መገናኛ ተቋማት የጋዜጠኝነት ሙያ ሥነ ምግባርን ተከትለው እንዲሠሩ የመገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን ጥሪ አቀረበ፡፡

199
ሁሉም የብዙኃን መገናኛ ተቋማት የጋዜጠኝነት ሙያ ሥነ ምግባርን ተከትለው እንዲሠሩ የመገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን ጥሪ አቀረበ፡፡
ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 09/2013 ዓ.ም (አሚኮ) ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የወጣውን አዋጅ ተላልፏል ያለውን አዲስ ስታንዳርድ ኦንላይን ሚዲያን ማገዱን አስታውቋል፡፡
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ በይፋዊ ማኅበራዊ ትስስር ገጹ እንዳስታወቀው አዲስ ስታንዳርድ ኦንላይን ሚዲያ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የወጣውን አዋጅ በመተላለፉ ጊዜአዊ እገዳ ተጥሎበታል፡፡
አዲስ ስታንዳርድ ኦንላይን ሚዲያ ጊዜያዊ እገዳው የተላለፈበት በባለስልጣኑ የክትትል ግኝቶች ፣ ቅሬታዎች እና ከሽብርተኛው ትህነግ ጋር ያለውን ግንኙነት ተከትሎ በመሆኑ ነው ተብሏል፡፡
በእነዚህ እና በሌሎች ተዛማጅ የሥነ ምግባር ጉድለቶች ጥልቅ ምርመራ የሚደረግ መሆኑን የጠቀሰው ባለሥልጣኑ ተጨማሪ እርምጃዎች ሊወሰድበት እንደሚችልም አስታውቋል፡፡
ሁሉም የብዙኃን መገናኛ ተቋማት የጋዜጠኝነት ሙያ ሥነ ምግባርን ተከትለው እና የሕግ የበላይነትን አክብረው እንዲሠሩም ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ጥሪ አቅርቧል፡፡
ባለስልጣኑ የፕረስ ነፃነት ከተጠያቂነት ጋር መሆኑን ሊሰመርበት ይገባል ብሏል፡፡
በየማነብርሃን ጌታቸው
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous article“እኔ ያልመራኋት ሀገር ትፈርሳለች የሚል እምነት ያለው አሸባሪው ጁንታ የሀገራችንን ህልውና ለመናድ እያደረገ ያለው ጥረት በሕዝባችን የጋራ ትግል እንደሚከሽፍ ጥርጥር የለንም” የደቡብ ብሔር ብሔረሰብ እና ሕዝቦች ክልል
Next article“…እኛ የታጠቀውንም ያልታጠቀውንም ካልመራን እና በየደረጃችን መውሰድ የሚገባንን ኀላፊነት ካልወሰድን ሕዝቡ የሕልውና አደጋ ውስጥ ይወድቃል” ኮሎኔል ማርዬ በየነ