በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን ሑመራ ከተማ ዝክረ ሐምሌ 5 እየተከበረ ነው።

228
በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን ሑመራ ከተማ ዝክረ ሐምሌ 5 እየተከበረ ነው።
ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 08/2013 ዓ.ም (አሚኮ) ሐምሌ 5 የአማራ ሕዝብ የነጻነት ተጋድሎ መሠረት ናት። የአማራ ሕዝብን የማንነት ጥያቄ ያነገቡ እንቁዎች ከአፋኙ ትህነግ መራሽ መንግሥታዊ የጭቆና ሥርዓት ጋር ትንቅንቅ የገጠሙበት ቀን ነው። አማራ የጀግንነት ክንዱን ያሳየበት ዕለትም ነው።
የአማራ ሕዝብ የዘመናት ጥያቄ እንዲመለስ ብዙ እህትና ወንድሞች መስዋእት ቢኾኑም የአማራ ሕዝብ የጠላትን አንገት ያስደፋበት እለትም ነበር – ሐምሌ 5።
ሐምሌ 5 የወያኔ የደኅንነት ክፍል የአማራ ሕዝብ የማንነት ጥያቄ ያነገቡትን ጀግኖች የሻቢያ ተላላኪዎች፣ የግንቦት 7 አስፈጻሚዎች፣ ሽፍቶች እና ሌሎች ታርጋዎችን በመለጠፍ በቁጥጥር ስር ለማዋል ጥረት አድርጎ የከሸፈበት እለት ነው።
የወልቃይት አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴዎችን በድብቅ አፍኖ ለመውሰድ ዘመቻ ተካሂዶ ሳይሳካ የከሸፈበት ታሪክ የሚዘክረው ቀን ነው።
ሐምሌ 5/2008 ዓ.ም ጎንደር ላይ የተለኮሰው ትግል እያደር መቀጣጠል ወደ መላው አማራና ኢትዮጵያ እያደገ ሄዶ ለ27 ዓመት በኢትዮጵያ ላይ የነበረው የጭቆና አገዛዝ ዳግም ላይመለስ ተሰናበተ።
በድል ቀኑ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ ለአማራ ልዩ ኀይል፣ ለአማራ ሚሊሻ እንዲሁም ለፌዴራል ፖሊስ በሕግ ማስከበር ዘመቻው ላስገኙት አንጸባራቂ ድል ምስጋና ቀርቦላቸዋል።
ዘጋቢ፡- ደጀኔ በቀለ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous article”የሀገር መከላከያ ሰራዊትና የፌደራል ፖሊስ የቀጠናውን ሰላም በማስጠበቅ የዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅ በአስተማማኝ ቁመና ላይ ይገኛል” ብርጋዴር ጄኔራል አለማየው ወልዴ
Next article“በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሠሩ የምርምርና የፈጠራ ሥራዎች ወደ ተግባር እንዲቀየሩ የሚያደርግ ሥርዓት ተቋማቱ መዘርጋት ይጠበቅባቸዋል” ዶክተር አሕመዲን መሐመድ