የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖት ተከታዮች በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ሠላማዊ ሰልፍ እያካሄዱ ነው፡፡

309

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን በሰሜን ሸዋ ዞን ደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ሰልፍ እያካሄዱ ነው፡፡ ሠልፉ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና በምዕመኗቹ ላይ የሚፈፀመው ግፍ እንዲቆም የሚጠይቅ ነው፡፡

በሰልፉ ላይ ‹‹በቤተ ክርስቲያንና በምዕመኖቿ ላይ የሚፈጸመው ግፍና መከራ ይቁም፡፡ በቤተ ክርስቲያንና ምዕመኖቿ ላይ ግፍ የፈጸሙት በሕግ ይጠየቁ፡፡›› የሚሉ መልዕክቶች እየተላለፉ ነው፡፡

ተመሳሳይ ዓላማ ያላቸው ሰልፎች በባሕር ዳር፣ ቢቸና፣ ፍኖተ ሠላም፣ ቡሬ፣ እንጅባራ፣ ደላንታ፣ መርዓዊ፣ ደብረ ማርቆስ፣ ማጀቴ፣ ጫጫ፣ ውጫሌ፣ ወልድያ፣ ላልይበላና ሌሎችም ከተሞች እየተካሄዱ ነው፡፡

ዘጋቢ፡- ኤልያስ ፈጠነ

ፎቶ፡- ኤልያስ ፈጠነ እና ዲያቆን አሰፋ ጌትነት

Previous articleዛሬ በባሕር ዳር እየተካሄደ በሚገኘው ሰልፍ ላይ ከታዩ ልዩ መልዕክቶች ውስጥ አንዱ ይህ ነው፡፡
Next articleሜን ሸዋ ዞን – አንጎለላና ጠራ ወረዳ – ጫጫ ከተማ