የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን እና የክልሉ ሥነ-ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ለህልውና ዘመቻው ድጋፍ አደረጉ፡፡

298
የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን እና የክልሉ ሥነ-ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ለህልውና ዘመቻው ድጋፍ አደረጉ፡፡
ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 06/2013 ዓ.ም (አሚኮ) የተቋማቱ ሠራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊና ክልላዊ ሁኔታዎች ላይ ውይይት አድርገዋል፡፡ በውይይታቸውም ተቋማቱና ሠራተኞቻቸው የክልሉን የጸጥታ መዋቅር ለማጠናከርና ለህልውና ዘመቻው የሚውል የአንድ ወር ደመወዛቸውን ድጋፍ ለማድረግ ወስነዋል፡፡
የአማራ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን እንደተቋም 5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉ ተገልጿል፡፡
የየተቋማቱ ሠራተኞች ከሚያደርጉት የገንዘብ ድጋፍ ባለፈ በግንባር በመሰለፍ የሕይወት መስዋእትነት ለመከፍል መዘጋጀታቸውንም ገልጸዋል።
አዘጋጅ:- ብሩክ ተሾመ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous article“የአውሮፓ ህብረት በትግራይ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ያሳለፈው ውሳኔ እየተካሄደ ባለው የማጣራት ሂደት ጣልቃ መግባት ነው” የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
Next article“በትግራይ ክልል በሚገኙ ኤርትራውያን ስደተኞች ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል” የተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን