የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖት ተከታዮች በደብረ ማርቆስ ሰልፍ እያካሄዱ ነው፡፡

300

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ሰልፍ እያካሄዱ ነው፡፡ ሠልፉ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና በምዕመኗቹ ላይ የሚፈፀመው ግፍ እንዲቆም የሚጠይቅ መሆኑን ነው የተገለጸው፡፡

በሰልፉ ላይ ‹‹በቤተ ክርስቲያንና በምዕመኖቿ ላይ የሚፈጸመው ግፍና መከራ ይቁም፡፡ በቤተ ክርስቲያንና ምዕመኖቿ ላይ ግፍ የፈጸሙት በሕግ ይጠየቁ›› የሚሉ መልዕክቶች እየተላለፉ ነው፡፡

ተመሳሳይ ዓላማ ያላቸው ሰልፎች በባሕር ዳር፣ ቢቸና፣ ፍኖተ ሠላም፣ ቡሬ፣ እንጅባራ፣ መርዓዊ፣ ደብረ ብርሃን፣ ማጀቴ፣ ጫጫ፣ ውጫሌ፣ ወልድያ፣ ቆቦ፣ ላልይበላ፣ ደባርቅና ሌሎችም ከተሞች እየተካሄዱ ነው፡፡

ዘጋቢ፡- ሰሎሞን ጥበቡ እና ጋሻዬ ጌታሁን -ከደብረ ማርቆስ

Previous articleበወልድያ ከተማ ሠላማዊ ሠልፍ እየተካሄደ ነው፡፡
Next articleባሕር ዳር