“ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ መምሕራን የሚያደርጉትን ድጋፍ ለማጠናከር ታቅዷል” የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር

98
“ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ መምሕራን የሚያደርጉትን ድጋፍ ለማጠናከር ታቅዷል” የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር
ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 03/2013 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ መምህራን ለታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ እያደረጉ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ ለማስቀጠል ማቀዱን ማኅበሩ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ መሰረት ከተጣለበት ጊዜ አንስቶ በማኅበርም ኾነ በግለሰብ ደረጃ የቦንድ ግዥ እንዲካሔድ በመሥራት የበኩሉን አስተዋጽኦ ሲያደርግ መቆየቱም ተገልጿል።
የማኅበሩ ፕሬዚዳንት ዶክተር ዮሐንስ በንቲ እንደተናገሩት፤ ማኅበሩ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እስኪጠናቀቅ ድረስ ድጋፉን በተጠናከረ መልኩ ለማድረገ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ነው። ለአብነትም በተጠናቀቀው ሳምንት የ250 ሺህ ብር የቦንድ ግዥ ፈጽሟል።
ዶክተር ዮሀንስ እንደሚሉት፤ በአዲሱ በጀት ዓመትም የትምህርት ማኅበረሰብ የቦንድ ግዥ እንዲፈጽምና በተጠናከረ መልኩ እንዲቀጥል ለማድረግ የተለያዩ ተግባራት ታቅደዋል።
በአሁኑ ወቅት ከመምህራን ባሻገርም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በራሱ ሀብትና ላብ የጀመረው ግንባታ እንዲጠናቀቅ ለማገዝ ሰፊ ተነሳሽነት እየታየ መሆኑንም አንስተዋል። በመሆኑም መንግሥት ይሕንን እድል በመጠቀም ሃብት የማሰባሰብ ሥራውን በተደራጀ መንገድ መቀጠል አለበት ያሉት ዶክተር ዮሐንስ፤ ለኅብረተሰቡም መረጃዎችን በወቅቱ ማቅረብ እንደሚገባ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን የኃይል ፍላጎት በማማሏት በኩል በርካታ ችግሮችን ይፈታል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት ፕሮጀክት ዕውን እንዲሆን በቀጣይም ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው የተጠቆመው።
በዓለም አቀፍ ደረጃም አሁን እየተካሔዱ ያሉ የዲፕሎማሲ ሥራዎችንም አጠናክሮ የመቀጠልን አስፈላጊነት አጽንኦ የሰጡት ዶክተር ዮሐንሰ፤ የተፋሰሱ ሀገሮች ከታላቁ ህዳሴ ግንባታ የተሻለ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ በማሳወቅ ረገድ ሰፊ ሥራ መሥራት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል። ኢዜአ እንደዘገበው፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous article“በትልቅ ሀገር ውስጥ ውስን ሎጂስቲክስ ይዞ ምርጫ ማከናውን ከባድ ቢሆንም መፍትሔ ማምጣትና ማረም የሚችሉ ባለሙያዎች በመኖራቸው ስድስተኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫን በስኬት ማከናውን ተችሏል” የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚዴቅሳ
Next articleከ15 በላይ ሊቀጳጳሳትንና በርካታ ሊቃውንትን ያፈሩት መምህር አክሊለ ብርሃን ኃይለሥላሴ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ፡፡