ከ250 ዓመታት በፊት የታተመ የመጽሐፍ ቅዱስ ቅጂ ለባሕል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር ተበረከተ፡፡

141
ከ250 ዓመታት በፊት የታተመ የመጽሐፍ ቅዱስ ቅጂ ለባሕል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር ተበረከተ፡፡
ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 02/2013 ዓ.ም (አሚኮ) ኪንግ ጀምስ ቅጂ በመባል በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚታወቀው ቀደምት ሙሉ የእንግሊዘኛ የመጽሐፍ ቅዱስ ቅጂ ምንጮች አንዱ የሆነው የ1769 እ.አ.አ የታተመው መጸሐፍ ቅዱስ ከአቶ ሳምሶን መኮንን ጣሰው ቤተሰብ ለቅርስ ጥናት እና ጥበቃ ባለስልጣን ተበርክቷል።
በርክክብ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የኢፌዴሪ ባሕል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር ዶክተር ሒሩት ካሳው ፣ የባሕል ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ብዙነሽ መሰረት እና የቅርስ ጥናት እና ጥበቃ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሙሉጌታ ፍስሐ መገኘታቸውን ከባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የማኅበራዊ ትስሰር ገጽ የተገኘ መረጃ ያመላክታል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleʺቢልኩበት ላከ ቢጠሩት እንቢ አለ፣ መውዜሩን በጫንቃው በወገቡ ሽጉጥ እያንከባለለ”
Next articleከቀረበው የአፈር ማዳበሪያ 75 በመቶ ለአርሶ አደሮች መሰራጨቱን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ገለጸ፡፡