
“በህዳሴ ግድብ ጉዳይ ከስምምነት መድረስ የሚያስችለው ትክክለኛው መድረክ አፍሪካ ሕብረት-መራሽ ድርድር ነው” የናይል
ተፋሰስ ሀገራት
ባሕር ዳር፡ ሰኔ 30/2013 ዓ.ም (አሚኮ) በህዳሴ ግድብ ጉዳይ ከስምምነት መድረስ የሚያስችለው ትክክለኛው አካሄድ አፍሪካ
ሕብረት-መራሽ ድርድር መሆኑን የናይል ተፋሰስ ሀገራት ገለጹ፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚስትር ደመቀ መኮንን በዛሬው ዕለት መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ካደረጉ
የተፋሰሱ ሀገራት አምባሳደሮች እና ዲፕሎማቶች ጋር ተወይተዋል፡፡
ውይይቱ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ያለበትን ሁኔታ በተመለከተ ለሀገራቱ ማብራሪያ ለመስጠት ያለመ
መሆኑን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m