በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ ሳያቋርጡ እያከናወኑ እንደሚገኝ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

174
በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ ሳያቋርጡ እያከናወኑ እንደሚገኝ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
ባሕር ዳር: ሰኔ 27/2013 ዓ.ም (አሚኮ) የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በማኅበራዊ የትስስር ገጹ እንዳመላከተው በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ ሳያቋርጡ እያከናወኑ እንደሆነ ሚኒስቴሩ ትግራይ ከሚገኙ ዓለምአቀፍ ተቋማት ጋር ባደረገው ክትትል አረጋግጧል።
የተለያዩ ዓለም ዓቀፍ ሚዲያዎችም ቦታው ድረስ በመገኘት የተማሪዎችን ድምጽ በመቅረጽ ለተማሪ ቤተሰብና ለመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ማሰማታቸውን በመግለጽ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ እየሰጠ ያለውን መረጃ በተጨባጭ ማስረጃ በማረጋገጣቸው ምስጋናውን አቅርቧል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleየአካባቢያቸዉን ሰላም ለማስጠበቅ ሲሉ ሕይወታቸውን ላጡ የፓሊስ፣ የሚሊሻ እና የልዩ ኀይል ቤተሰቦች የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን የዋግ ልማት ማኀበር አስታወቀ።
Next article“የግብር ሥራ ገንዘብ የመሠብሠብ ጉዳይ ብቻ አለመሆኑን በመረዳት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ውጤታማ ግብር አሰባሰብ እንዲኖር ጠንካራ ተሳትፎ ማድረግ ይገባል” የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኀላፊ ብዙዓየሁ ቢያዝን