“ፖሊስነት ለሕዝብና ለሀገር ጥቅምና ክብር ሲባል ራስን አሳልፎ በመስጠት መስዋእትነት የሚከፈልበት ክቡር ሙያ ነው”

235
“ፖሊስነት ለሕዝብና ለሀገር ጥቅምና ክብር ሲባል ራስን አሳልፎ በመስጠት መስዋእትነት የሚከፈልበት ክቡር ሙያ ነው”
ባሕር ዳር፡ ሰኔ 27/ 2013 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሌጅ ልዩ መደበኛ ምልምል ፖሊሶችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል።
በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ ለ1ኛ ዙር ልዩ መደበኛ ምልምል ፖሊሶች መልዕክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሌጅ ዋና ዳይሬክተር ምክትል ኮሚሽነር አንማው አለሜ ወቅቱ የሥነልቦና ዝግጅት እና የአካል ብቃት የሚጠይቅ በመሆኑ የጸጥታ አካላት ሕዝባዊ ወገንተኝነታቸውን ይበልጥ ማጠናከር ይገባቸዋል ብለዋል። ከምንጊዜውም በላይ እርስ በእርስ በመግባባት ሀገርን እና ሕዝብን ማዳን ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
“ፖሊስነት ለሕዝብና ለሀገር ጥቅምና ክብር ሲባል ራስን አሳልፎ በመስጠት መስዋእትነት የሚከፈልበት ክቡር ሙያ ነው” ነው ያሉት ምክትል ኮሚሽነሩ። ተመራቂዎች በተሰማሩበት የሙያ መስክ የክልሉን ሰላም በመጠበቅና ለሀገራችን እድገት የበኩላቸውን እንዲወጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ምክትል ኮሚሽነሩ በአመለካከት እና በሥነምግባር ጠንካራ አቋም በመያዝ በገቡት ቃል መሰረት የጸጥታ አካላት ሕብረተሰቡን ማገልገል እንደሚገባቸውም ተናግረዋል።
ተመራቂዎችም በተሰጣቸው ስልጠና ብቁ መሆናቸውንና በገቡት ቃል መሠረት ወንጀልን ለመከላከል በቁርጠኝነት እንደሚሠሩ እና መስዋእትነት ለመክፈል መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
ዘጋቢ፦ አማረ ሊቁ – ከደብረ ማርቆስ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleየተናጠል ተኩስ አቁም እና የመከላከያን ከመቀሌ መውጣት ተከትሎ የሕወሓት የሽብር ቡድን በመቀሌ እና በሌሎች የትግራይ ከተሞች በነዋሪዎች ላይ የተለያዩ ጥቃቶችን እያደረሰ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡
Next article“የኢትዮጵያ የርህራሄ ተምሳሌት የነበሩት አበበች ጎበናን ህልፈተ ህይወት ስሰማ እጅግ አዝኛለሁ” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር)