ኢትዮጵያ የተሰረቁ ቅርሶቿን ከኔዘርላንድ ልታስመለስ ነው፡፡

100
ኢትዮጵያ የተሰረቁ ቅርሶቿን ከኔዘርላንድ ልታስመለስ ነው፡፡
ባሕር ዳር፡ ሰኔ 25/2013 ዓ.ም (አሚኮ) ቅርሶቹ ከ15ኛው ክፍለ ዘመን በፊት የነበሩ ሦስት ጥንታዊ መጻሕፍቶችን ያካትታል፡፡ ቅርሶቹ ባለፈው ሳምንት ለሽያጭ ጨረታ ቀርበው ነበር፤ በኔዘርላንድ ዘሄግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጨረታውን ያቀረቡትን አካላት እንዲያቆሙ በመጠየቅ እንዲታገዱ አድርጓል፡፡
ኤምባሲው እንዳለው ጨረታው ታግዷል፤ ቅርሶቹም ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱ ገልጿል፡፡
በኔዘርላንድ ዘሄግ የኢትዮጵያ አምባሰደር ሚሊዮን ሳሙኤል ቅርሶቹ በመመለሳቸው መደስታቸውን ተናግረዋል፡፡
ቅርሶቹ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ እየተሠራ እንደሚገኝ መግለጻቸውን ከኤምባሲው የተገኘ መረጃ ያመላክታል፡፡
በታዘብ አራጋው
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous article“መንግሥት የሕግ ማስከበር ግዳጁን በብቃት በመወጣት አጀንዳውን ወደ ሌላ ቀዳሚ ተልዕኮ ማድረጉ የተሻለ ወታደራዊ ስልት ነው” በውትድርና ኢትዮጵያን ያገለገሉ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች
Next articleጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ 100ኛ የምስረታ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ፡፡