ኢትዮጵያ ተግባራዊ ያደረገችው የተናጠል የተኩስ አቁም አዋጅ ተሰፋ ሰጪ እርምጃ ነው ስትል ሩሲያ አስታወቀች፡፡

171
ኢትዮጵያ ተግባራዊ ያደረገችው የተናጠል የተኩስ አቁም አዋጅ ተሰፋ ሰጪ እርምጃ ነው ስትል ሩሲያ አስታወቀች፡፡
ባሕር ዳር፡ ሰኔ 24/ 2013 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ መንግሥት በቅርቡ በትግራይ ክልል ተግባራዊ ያደረገው የተናጠል የተኩስ አቁም ውሳኔ በክልሉ ላይ ለውጥ ለማምጣት ተሰፋ ሰጪ እርምጃ መሆኑን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሩሲያ ቋሚ ተወካይ አምባሳደር ቫሲሊ ኔቤንዚያ ገለጹ፡፡
አምባሳደሩ በሰጡት ወርሃዊ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት በክልሉ እያደረገ ላለው ከፍተኛ የሰብዓዊ ድጋፍ እውቅና ሊሰጠው ይገባል ብለዋል።
ሌሎች ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ድጋፍ ሰጪ ተቋማትም ድጋፍ ሊያደርጉ የሚችሉበት መንገድ ሊመቻቻልቸው እንደሚገባ አምባሳደሩ በዚሁ መግለጫቸው ላይ አስታውቀዋል። ዘገባው የኢፕድ ነው
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous article“አሸባሪው ህወሃት ከስልጣን ውጪ ለትግራይ ሕዝብ ጥቅምና ህልውና ዴንታ እንደሌለው በተግባር አሳይቷል” ዶክተር አረጋዊ በርሄ
Next articleባለፉት አስራ እንድ ወራት ከዲያስፓራው በድጋፍ መልክ አንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር መገኘቱን የኢትዮጵያ ዲያስፓራ ኤጀንሲ አስታወቀ።