በትግራይ ክልል የሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ለማስወጣት እየተሠራ ነው።

216
በትግራይ ክልል የሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ለማስወጣት እየተሠራ ነው።
ባሕር ዳር: ሰኔ 24 ቀን 2013 ዓ.ም (አሚኮ) በትግራይ ክልል የሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ለማስወጣት እየተሠራ መሆኑን የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።
የሚኒስቴሩ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ወይዘሮ አመለወርቅ ህዝቅኤል እንደተናገሩት ሚኒስቴሩ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመምከር ተማሪዎቹን ለማስወጣት ትራንስፖርት እያመቻቸ ይገኛል።
ተማሪዎቹ ደኅንነታቸው ተጠብቆ እንዲወጡ ተገቢው ዝግጅት እየተደረገና ሁኔታዎችን እያመቻቸ ይገኛል ነው ያሉት።
ወላጆችም በማኅበራዊ ሚዲያዎች የሚወጡ ሐሰተኛ መረጃዎች ሳይረብሿቸው እንዲጠባበቁ ወይዘሮ አመለወርቅ መጠየቃቸውን ፋብኮ ዘግቧል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleኢትዮጵያና ደቡብ ኮሪያ ያላቸውን ዘርፈ ብዙ ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር አስፈላጊ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ገለጹ።
Next article“አሸባሪው ህወሃት ከስልጣን ውጪ ለትግራይ ሕዝብ ጥቅምና ህልውና ዴንታ እንደሌለው በተግባር አሳይቷል” ዶክተር አረጋዊ በርሄ