ኢትዮጵያ እና እስራኤል የኮሮናቫይረስ ክትባትን በጋራ ሊያመርቱ መሆኑ ተገለጸ፡፡

142
ኢትዮጵያ እና እስራኤል የኮሮናቫይረስ ክትባትን በጋራ ሊያመርቱ መሆኑ ተገለጸ፡፡
ባሕር ዳር፡ ሰኔ 24/2013 ዓ.ም (አሚኮ) ኢትዮጵያ እና እስራኤል የኮሮናቫይረስ ክትባትን በጋራ በኢትዮጵያ ሊያመርቱ መሆኑ ተገልጿል፡፡
በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አለልኝ አድማሱ፣ ምክትል አምባሳደር ኦር ዳንኤሊ እና የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በጤናው ዘርፍ አብሮ በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል።
ኢትዮጵያ እና እስራኤል በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ ክትባት በጋራ ለማምረት በሚቻልበት ሁኔታ፣ የአቅም ግንባታ፣ የጤና ዘርፍ ኢንቨስትመንት እና በሁለቱ ሀገራት ጤና ሚኒስቴር መካከል ትብብር ለማሳደግ የሚያስችል ውይይት ማድረጋቸውን ኢብኮ ዘግቧል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous article“የፌዴራል መንግሥት የመተከል ዞን ተፈናቃዮችን በዘላቂነት ለማቋቋም ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ይዟል” የመተከል ዞን ኮማንድ ፖስት ቴክኒክ ኮሚቴ
Next article“መከላከያ ሠራዊት ከትግራይ መውጣቱን ተከትሎ መንግሥታት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት በጎ ምላሽ መስጠት ጀምረዋል” የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር