28 ታዳጊ ኢትዮጵያውያን ከታንዛኒያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ፡፡

103
28 ታዳጊ ኢትዮጵያውያን ከታንዛኒያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ፡፡
ባሕር ዳር፡ ሰኔ 22/2013 ዓ.ም (አሚኮ) በህገወጥ ስደት ወደ ደቡብ አፍሪካ ለሚደረግ ጉዞ ከሀገር ወጥተው የታንዛኒያን ድንበር ጥሰው ሲገቡ በሀገሪቱ ፖሊስ ተይዘው የነበሩ 28 ኢትዮጵያውያን ታዳጊዎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡
ታዳጊዎቹ ከሌሎች ከ18 ዓመት በላይ ከሆኑ 36 ስደተኞች ጋር ተይዘው የነበሩ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
ይህን ተከትሎ የታንዛኒያ መንግሥት እድሜያቸው አነስተኛ የሆኑትን ለማሰር የማይችል በመሆኑ በአፋጣኝ ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ ኤምባሲው ሁኔታውን እንዲያመቻች ባቀረበው ጥያቄ መሰረት ቅድሚያ ተሰጥቷቸው የተመለሱ መሆኑን በታንዛኒያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ያወጣው መረጃ ያመላክታል።
በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ዜጎች በታንዛኒያ እስር ቤቶች በእስራት ላይ የሚገኙ በመሆኑ ኹሉንም ዜጎች ወደ ሀገር ቤት ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት በመደረግ ላይ እንደሚገኝ ኤምባሲው አመላክቷል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleየአባይ ተፋሰስ ሀገራትን መሰረት አድርጎ አንድ ቢሊየን ችግኝ በጎረቤት ሀገራት ለመትከል መታቀዱን አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገለጹ፡፡
Next article‹በዕውቀትና በክዕሎት የበለጸገ ዜጋ ማፍራት ካልተቻለ የሀገርን ልማት እና ስልጣኔ ማረጋገጥ አይቻልም›› የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ንጉስ ታደሰ