የመለስ ዜናዊ የአመራር አካዳሚ የአፍሪካ የአመራር ልህቀት ማዕከል በሚል ስያሜውን በይፋ ዛሬ ይቀይራል።

490

የመለስ ዜናዊ የአመራር አካዳሚ የአፍሪካ የአመራር ልህቀት ማዕከል በሚል ስያሜውን በይፋ ዛሬ ይቀይራል።

ባሕር ዳር፡ ሰኔ 19/ 2013 ዓ.ም (አሚኮ) የቀድሞ የመለስ ዜናዊ የአመራር አካዳሚ ይባል የነበረውን ተቋም ስያሜ የአፍሪካ የአመራር ልህቀት ማዕከል በሚል እንዲሰየም የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሰኔ 15/2013 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል፡፡

የአካዳሚው የስም ለውጥ የ21ኛው ክፍለ ዘመን የአመራር ጥያቄዎችን ማሟላት የሚያስችል አቅም ያላቸውን ልሂቃን የሚያፈራ መሆኑን ይገልጻል ተብሏል፡፡

የዕድገት ተኮር አስተሳሰብን የሚያንፀባርቅ የትምህርት ተቋም ማድረግን በሚመጥን እና በሚገልጽ መልኩ በአዲስ እንደተደራጀም ተገልጿል፡፡

ዛሬ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በተገኙበት በስሉሉታ ከተማ ያስገነባው አዲስ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ በይፋ ይመረቃል ተብሎ ይጠበቃል።

ዘጋቢ፡- ጋሻው ፋንታሁን

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

Previous articleበትግራይ ክልል የአሸባሪው ሕወሓት ርዝራዥ በሚንቀሳቀስበት አካባቢ የሰብዓዊ ድጋፍ በሚያደርጉ ሁለት ኢትዮጵያን እና አንድ ስፔናዊት ላይ ጥቃት ተፈጸመ።
Next articleከሳዑዲ አረቢያ ዜጎችን ወደ ሀገር መመለስ እንደሚጀመር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡