
“የመለስ ዜናዊ የአመራር አካዳሚ” “የአፍሪካ የአመራር ልህቀት ማዕከል” በሚል እንዲሰየም የሚኒስትሮች ምክር ቤት አጸደቀ።
ባሕር ዳር: ሰኔ 15/2013 ዓ.ም (አሚኮ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት “የመለስ ዜናዊ የአመራር አካዳሚ” “የአፍሪካ የአመራር ልህቀት ማዕከል” በሚል እንዲሰየም ዛሬ አጽድቋል፡፡
አካዳሚው ከስም ለውጥ ጋር የ21 ኛው ክፍለዘመን የአመራር ጥያቄዎችን ለማሟላት የሚያስችል አቅም ያላቸውን ልሂቃን የሚያፈራ እና የዕድገት ተኮር አስተሳሰብን የሚያንፀባርቅ የትምህርት ተቋም እንዲሆን ያለመ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ.ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ አመላክተዋል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m