ኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ መዋዕለ ነዋይ ፍሰትን በመሳብ ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራ ቀዳሚ መሆኗ ተገለጸ፡፡

182

ባሕር ዳር፡ መስከረም 9/2012 ዓ.ም (አብመድ) በአውሮፓውያኑ 2019 ኢትዮጵያ ትልቁን የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት በማስተናገድ ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራት በቀዳሚነት መቀመጧ ነው የተገለጸው፡፡

እንግሊዙ ኩባንያ ‹ኧርነስት እና ያንግ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ማማከር አገልግሎት› ባሰራጨው መረጃ እንዳለው በምሥራቅ አፍሪካ ከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ 7 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የውጭ ቀጥታ መዋዕለ ንዋይ ስባለች፡፡

ኬንያ 2 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር መዋዕለ ንዋይ ስትስብ ታንዛኒያ 1 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር በመሳብ ይከተላሉ፡፡

ምንጭ፡- አፍሪካ ኒውስ

በኪሩቤል ተሾመ

Previous articleየኢትዮ-ቴሌኮም የሰሜን ሰሜን ምዕራብ ሪጅን በጎንደር ከተማ ለሚገኙ ሁለት ትምህርት ቤቶች የደብተርና የልዩ ልዩ ቁሳቁሶች ድጋፍ አደረገ።
Next articleባለፈው በጀት ዓመት 138 ሚሊዮን ብር ወደ መንግሥት ካዝና ገቢ መደረጉ ተገለጸ፡፡