በምርጫ ሂደቱ ሕገ ወጥ ተግባራት የሚፈጽሙ አካላት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ምርጫ ቦርድ አሳሰበ፡፡

219
በምርጫ ሂደቱ ሕገ ወጥ ተግባራት የሚፈጽሙ አካላት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ምርጫ ቦርድ አሳሰበ፡፡
ባሕር ዳር፡ ሰኔ 14/ 2013 ዓ.ም 6ኛው ሀገራዊ እና ከልላዊ ምርጫ ዛሬ ከንጋቱ 12፡00 ጀምሮ በሀገሪቱ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
ይሁን እንጅ በአንድ አንድ ቦታዎች ሕገወጥ ተግባራት መኖራቸውን የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ተናግረዋል፡፡
ወይዘሪት ብርቱካን በአማራ እና በደቡብ ክልል የሚገኙ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የእጩ ተወዳዳሪ ወኪሎቻቸውን ማንቀሳቀስ እንዳልቻሉ ሪፖርት ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡
የታችኛው የአስተዳድር መዋቅር ችግሩን መፍታት እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡
ችግሩን ለመፍታት እየተሠራ መኾኑንም ጠቁመዋል፡፡ በምርጫው ሂደት ሕገ ወጥ ተግባራትን የሚፈጽሙ አካላት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡም አሳስበዋል፡፡
በትርንጎ ይፍሩ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleየአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ(አብን) የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጣሂር ሙሐመድ የምርጫ ካርድ ባወጡበት በጎንደር ዙሪያ ምርጫ ክልል 4 በእንፍራንዝ ከተማ ቀጠና 5 ምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምጽ ሰጥተዋል፡፡
Next article‹‹ችግኝ እየተከልን ዴሞክራሲንም እንተክላለን›› ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ.ር)