በኖርዌይ ኦስሎና አካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን የአሜሪካ መንግሥት በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ላይ ያስተላለፈውን ውሳኔ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ አካሄዱ፡፡

176
በኖርዌይ ኦስሎና አካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን የአሜሪካ መንግሥት በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ላይ ያስተላለፈውን ውሳኔ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ አካሄዱ፡፡
ባሕር ዳር፡ ግንቦት 23/2013 ዓ.ም (አሚኮ) በኖርዌይ ኦስሎና አካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን በጋራ የአሜሪካ መንግሥት በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ላይ ኢ-ፍትሐዊ በሆነ ሁኔታ ያስተላለፈውን ውሳኔ በመቃወም በኦስሎ የአሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት በመገኘት የተቃውሞ ሰልፍ አካሂደዋል።
በኖርዌይ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ለማ ደስታ የአሜሪካ መንግሥት በኢትዮጵያና ኤርትራ ላይ ያስተላለፈው ውሳኔ ጣልቃ ገብነትና ከሉዓላዊነት ጋር የሚፃረር አደገኛ አካሄድ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ ላይ የተሳሳተ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲዋን እያራመደች በመሆኑ ይሄንኑ በአፋጣኝ እንድታሻሽል፣ የአሜሪካ ሴኔት በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ላይ በአሸባሪው ሕወሓት በሚነዛው የተሳሳተ መረጃ ላይ በመመርኮዝ ያስተላለፈውን ውሳኔ ያለቅድመ ሁኔታ እንዲነሳ ሰልፈኞቹ ጠይቀዋል፡፡
ሰልፈኞቹ የአሜሪካ መንግሥት በሀገራቱ ጉዳይ ላይ እያሳደረ ከሚገኘው ጫና እንዲቆጠብ የተፃፈ የተቃውሞ ደብዳቤ ኦስሎ ለሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ጉዳይ ፈፃሚ ማስረከባቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል ዐቀባይ ጽሕፈት ቤት የተገኘ መረጃ ያመላክታል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous article“ከኢትዮጵያ ጥቅም በተጻራሪ የቆሙ ኃይሎች የሚያራምዱትን የተደራጀና የተቀናጀ ጫና ለመቋቋም ከመንግሥትም ሆነ ከዳያስፖራው ብዙ መሥራት ይጠበቃል” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን
Next articleየቅጥር ማስታወቂያ