ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዝዳንት ፌሊክስ ሲሼኬዲ ጋር ተወያዩ።

118
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዝዳንት ፌሊክስ ሲሼኬዲ ጋር ተወያዩ።
ባሕር ዳር: ግንቦት 03/2013 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) የወቅቱን የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር እና የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዝዳንት ፌሊክስ ሲሼኬዲ እንዲሁም የልዑካን ቡድናቸውን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡
በውይይቱም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ኢትዮጵያ “ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔዎች” በመፈለግ እና በአሁኑ የሕብረቱ ሊቀመንበር አመቻችነት በአፍሪካ ሕብረት በሚመራው የሦስትዮሽ ድርድር ሂደት ቁርጠኛ መሆኗን በአጽንዖት ተናግረዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ታላቁ የህዳሴ ግድብ በታችኛው ተፋሰስ ሀገራት መካከል የትብብር እና የጋራ ልማት ተምሳሌት ሊሆን እንደሚችል እና በሁለቱም ሀገራት ላይ ምንም ጉዳት በማያስከትል መንገድ እንደሚከናወን ኢትዮጵያ ያላትን ጽኑ አቋም አስረድተዋል፡፡
በትብብር መርህ ማዕቀፍ (ዴክላሬሽን ኦፍ ፕሪንሲፕልስ) መሠረት ለሁሉም ወገኖች የሚጠቅም ስምምነት ላይ እንዲደረስ ኢትዮጵያ ፍላጎት እንዳላት መገለጹን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የተገኘ መረጃ ያመላክታል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous article“የኢድ አል ፈጥር በዓል ሲከበር በዘር ፖለቲካና ቀውስ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በጊዜአዊ መጠለያ የሚገኙ ወገኖችን በማሰብና በመደገፍ ሊሆን ይገባል” የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት
Next article“መጪው ጊዜ ክረምት በመሆኑ ሁኔታው የከፋ እንዳይሆን ለተፈናቃዮች መጠለያ ለመገንባት ቁሳቁስ እየሰበሰብን ነው” ‹‹እኔ እያለሁ ወገኔ አይራብም›› የኮምቦልቻ ከተማ በጎፈቃደኛ ወጣቶች