አርቲስት መሀሪ ደገፋው ፋሲል ከነማን ለመደገፍ ዛሬ ቃል ገብቷል ፡፡ አርቲስቱ ሰሞኑን ከሚኖርበት አሜሪካ ሀገር ወደ ኢትዮጵያ ገብቷል፡፡

405

ባሕር ዳር፡ ታኅሳስ 24/2011ዓ.ም (አብመድ) አርቲስት መሀሪ ደገፋው ፋሲል ከነማን ለመደገፍ ዛሬ ቃል ገብቷል ፡፡
አርቲስቱ ሰሞኑን ከሚኖርበት አሜሪካ ሀገር ወደ ኢትዮጵያ ገብቷል፡፡

Image may contain: one or more people, people standing and outdoor

ፋሲል ከነማን ለመደገፍም ቅዳሜ በጎንደር በሚደረግ ኮንሰርት አንዱን ትኬት በ50 ሺህ ብር በመግዛት ለክለቡ ገቢ እንደሚያደርግ ተናግሯል፡፡ ክለቡን ለመደገፍ ከሚሰራ ማንኛውም አካል ጋር በመሆን እንደሚሰራም ገልጿል፡፡

አርቲስት መሀሪ በኢትዮጵያ በሚኖረው ቆይታ ከአርቲስት ይሁኔ በላይ ጋር በመሆን ፍቅር ያሸንፋል ኮንሰርትን በተለያዩ ከተሞች ያካሂዳል፡፡ ኮንሰርቱም የፊታችን ቅዳሜ በጎንደር ይጀምራል፡፡

ዘጋቢ፡-ንዋይ ሙሉጌታ

Previous articleአዴፓ በአዲስ አበባ የባለቤትነት ጉዳይ ላይ ጠንካራ አቋም እንዳለው አስታወቀ፡፡
Next articleትናንት ምሽት በተካሄደው የካራባዎ ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ በኢትሀድ ብሪቶን አልቢዮንን የጋበዘው ማንቸስተር ሲቲ በከፍተኛ የጨዋታ ብልጫ 9ለ0 አሸንፏል፡፡