የዓድዋ ተጓዦች የመዝጊያ መርኃ ግብር በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

361
የዓድዋ ተጓዦች የመዝጊያ መርኃ ግብር በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።
ባሕር ዳር፡ መጋቢት 02/2013 ዓ.ም (አብመድ) 125ኛውን የዓድዋ ድል ለመዘከር መነሻቸውን አዲስ አበባ አድርገው መዳረሻቸውን ደግሞ አድዋ ተራሮችን ያደረጉ 125 ወጣቶች (107 ወንዶችና 18 ሴቶች) ጥር 9/2013 ነበር ከአዲስ አበባ የተሸኙት፡፡ ተሳታፊዎቹ ከ1 ሽህ ኪሎ ሜትር በላይ የእግር ጉዞ አድርገዋል፡፡ ተጓዦቹ ወደ አዲስአበባ መመለሳቸውን ተከትሎ የማጠናቀቂያ መዝጊያ መርኃ ግብር በጣይቱ ሆቴል እየተካሄደ ነው።
በመርኃ ግብሩ አርቲሰትና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ታማኝ በየነ፣ አርቲሰት ዓለም ጸሐይ ወዳጆን ጨምሮ በርካታ አርቲስቶች፣ አርበኞችና ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፈውበታል።
ዘጋቢ፡- እንዳልካቸው አባቡ – ከአዲስ አበባ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleባለፉት ስድስት ወራት ከ144 ሺህ በላይ ዜጎች የንፁህ መጠጥ ውኃ ተጠቃሚ መሆናቸውን የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ፡፡
Next articleከ8 ሺህ በላይ እጩዎችን መመዝገቡንና ሕጋዊ ሰውነት ያላቸው ፓርቲዎች 49 የምርጫ መወዳደርያ ምልክቶችን መውሰዳቸውን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ገለጸ።