የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ስምንት የመንገድ ፕሮጀክቶችን የኮንትራት ስምምነት ተፈራረመ።

1882
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ስምንት የመንገድ ፕሮጀክቶችን የኮንትራት ስምምነት ተፈራረመ።
ባሕር ዳር፡ ጥር 26/2013 ዓ.ም (አብመድ) በተያዘው 2013 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የ13 የመንገድ ፕሮጀክቶች የኮንትራት ስምምነት መፈራረሙን ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ አስታውቋል። በበጀት ዓመቱ በ43 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በጀት ወጪ 21 የመንገድ ፕሮጀክቶች ሥራ ይጀመራል ተብሏል።
እንደ ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ መረጃ የመንገድ ፕሮጀክቶቹ ሥራ 1 ሺህ 774 ኪሎ ሜትር ርዝመት ይሸፍናል። ዛሬ የተፈረሙት የመንገድ ፕሮጀክቶች መካከል በአማራ ክልል ለረጅም ዓመታት ደረጃቸው እንዲሻሻል በሕዝብ ጥያቄ ሲቀርብባቸው ነበሩ አካባቢዎችን አካቷል፡፡
ደብረ ማርቆስ – ደብረ ኤልያስ – ተምጫ – ቁጭ – አየሁ – ዚገም – ቻግኒ ኮንትራት ሦስት ቁጭ – አምበላ መንገድ ፕሮጀት ጠቅላላ 78 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር አንዱ ነው፡፡
ዱርቤቴ-ቁንዝላ-ገላጎ-መተማ፣ ሎት ሦስት ገላጎ-ገንዳ ውኃ መንገድ ዲዛይንና ግንባታ ሥራም 125 ኪሎ ሜትር ይገኝበታል፡፡
73 ኪሎ ሜትር ዳንግላ – ጃዊ ዲዛይንና ግንባታ መንገድ ሥራ ፕሮጀክትም በስምምነቱ ተካቷል፡፡ 35 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር ማንኩሳ – ብርሸለቆ -142 ቀበሌ ዲዛይንና ግንባታ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት በስምምነቱ ከተካተቱት ውስጥ ይገኝበታል፡፡
በተደረገው ስምምነት እንደስላሴ – ራማ ገረሁ ሰናይ ፕሮጀክት ከኤርትራ፣ ዱርቤቴ – ቁንዝላ – ገላጎ – መተማ ከሱዳን፣ ነጌሌ ቦረና – ዶሎ አዶ – መልካ ኩፍቱ ከኬንያና ሶማሊያ የሚያገናኙ ናቸው ተብሏል።
በዓመቱ ከሚገነቡ 21 ፕሮጀክቶች ውስጥ 20ቹ በኢትዮጵያ መንግሥት ወጪ የሚገነቡ መሆናቸውም ተገልጿል።
ዘጋቢ፡- ዘመኑ ታደለ – ከአዲስ አበባ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleበትራንስፖርት ስምሪት ችግር ሥራቸውን በሚፈልጉት ጊዜና ፍጥነት ለማከናወን መቸገራቸውን ተሳፋሪዎች ተናገሩ፡፡
Next articleበባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር በጣና ክፍለ ከተማ በሕገ ወጥ መንገድ በግለሰብ ቤት የተከማቸ 11 በርሚል ነዳጅ እና ቤንዚን በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡