በኢትዮጵያ እና ሱዳን የድንበር ጉዳይ ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት ተካሄደ፡፡

234
በኢትዮጵያ እና ሱዳን የድንበር ጉዳይ ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት ተካሄደ፡፡
ባሕር ዳር፡ ጥር 21/2013 ዓ.ም (አብመድ) በአዲስ አበባ የተካሄደው አውደጥናቱ በዋናነት ለበርካታ ዓመታት በኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር ሲካሄድ የቆየውን የድንበር ዳግም ማካለል ጉዳይ በነባር የሁለትዮሽ መድረኮች በሰላማዊና በዘላቂ መልኩ መፍታት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ነው ምክክር የተደረገው፡፡
በአውደጥናቱ ላይ የድንበር ጉዳዩን በተመለከተ የተቋቋሙት የዓለምአቀፍ የሕግ ባለሙያዎች እና ብሔራዊ የጥናትና ምርምር ባለሙያዎች ቡድን አባላት ተሳትፈዋል፡፡
በተካሄደው አውደጥናት በድንበር ዳግም ማካለል ዙሪያ ሙያዊ ውይይት ተደርጓል።
በሃገራቱ መካከል ያለው የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር፣ የታሪክ እና ሌሎች ዘርፈ ብዙ ግንኙነቶች ተጠናክረው በሚቀጥሉበት ሁኔታ ላይ ውይይት መደረጉን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል ዐቀባይ ጽሕፈት ቤት የተገኘ መረጃ ያመላክታል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleየመሬት ወረራ ሲፈፀም ኃላፊነታቸውን ባልተወጡ በየደረጃው ያሉ የሥራ ኃላፊዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ፡፡
Next articleበሦስት ቀናት ውስጥ ከ270 ሺህ በላይ ሴቶች የማህፀን በር ጫፍ ካንሰር መከላከያ ክትባት እንደወሰዱ የአማራ ክልል ጤና ጥበቃ ቢሮ አስታወቀ፡፡