የጥምቀት በዓል በጎንደር ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲከበር በቂ ዝግጅት ማድረጉን የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ፡፡

190
የጥምቀት በዓል በጎንደር ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲከበር በቂ ዝግጅት ማድረጉን የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ፡፡
ባሕር ዳር፡ ጥር 08/2013 ዓ.ም (አብመድ) በጎንደር የጥምቀት በዓልን ለማክበር ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ የሚመጡ እንግዶችን የከተማዋ ነዋሪዎች መቀበል ጀምረዋል፡፡
በዓሉ ያለምንም የጸጥታ ችግር በድምቀት እንዲከበርም የከተማዋ ነዋሪዎች ከጸጥታ አካላት ጋር ውይይት ማድረጋቸውን የፖሊስ መምሪያው ኀላፊ ኮማንደር አየልኝ ታከለ ተናግረዋል፡፡
የተለያዩ የወጣት አደረጃጀቶችና ሲቪክ ማህበራትም የጥምቀት በዓልን ለማክበር የሚመጡ እንግዶች ተደስተውና የሰላም ችግር ሳይገጥማቸው በዓሉን እዲያሳልፉ ለማድረግ ከፀጥታ አካላት ጋር በጋራ እየሠሩ ነው ብለዋል ኮማንደር አየልኝ፡፡
የከተማ አስተዳድሩ ሰላም እና ሕዝብ ደኀንነት መምሪያ ኃላፊ አቶ ናትናኤል ጎሹ እደገለፁት በበዓሉ ከጸጥታ አካሉ ውጭ በከተማዋ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ አይቻልም፡፡ ለደስታ መግለጫ በሚል ሮኬትም ሆነ እርችት መተኮስም የተከለከለ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
ዘጋቢ፡- ምስጋናው ብርሃኔ-ከጎንደር
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በፌስቡክ https://bit.ly/2UwIpCw
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleየመቅደላ ዓምባ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን ተማሪዎች ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ እያስመረቀ ነው፡፡
Next articleኢትዮጵያን በቀጣይ 10 ዓመታት የአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ ተመራቂ ተማሪዎች በሀገሪቱ ልማት በመሳተፍ የድርሻቸውን እንዲወጡ የጠቅላይ ሚንስትሩ የደኅንነት አማካሪ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው ጥሪ አቀረቡ፡፡