ርእሰ መሥተዳድር አገኘሁ ተሻገር በማእከላዊ ጎንደር ዞን በላይ አርማጭሆ ወረዳ እየተከናወኑ ያሉ የችግኝ ዝግጅትና የተፋሰስ ልማትን እየጎበኙ ነው።

458
ርእሰ መሥተዳድር አገኘሁ ተሻገር በማእከላዊ ጎንደር ዞን በላይ አርማጭሆ ወረዳ እየተከናወኑ ያሉ የችግኝ ዝግጅትና የተፋሰስ ልማትን እየጎበኙ ነው።
ባሕር ዳር፡ ጥር 04/2013 ዓ.ም (አብመድ) ርእሰ መሥተዳድሩ በወረዳው በሹማራ ሎምየ ቀበሌ የባንብላ ተፋሰስ ልማትን ተመልክተዋል።
ባለፉት ዓመታት በተከናወነው የተፋሰስስ ልማት ሥራ ቡና፣ ማንጎ፣ ሙዝ፣ጌሾና ሌሎች ገበያ ተኮር አትክልትና ፍራፍሬ በአካባቢው አርሶ አደሮች እየለማ ይገኛል።
አርሶ አደር ተስፋ ኃይሌና ብርሃን ፈንቅለው እንዳሉት እነርሱን ጨምሮ በርካታ አርሶ አደሮች ተግባራዊ ባደረጉት የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው።
ርእሰ መሥተዳድሩ የ2013 ዓ.ም የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ሥራንም በማእከላዊ ጎንደር ዞን በላይ አርማጭሆ ወረዳ በይፋ ያስጀምራሉ።
በተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ሥራ ማስጀመሪያው የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አገኘሁ ተሻገር፣ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወርቀሰሙ ማሞና የኢፌዴሪ ግብርና ሚኒስትር ዲኤታ ሳሚ ረዲን ጨምሮ የፌዴራል፣ የክልል እና የዞን ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡- ስማቸው እሸቴ – ከላይ አርማጭሆ
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleየግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባ ምርትን የመተካት ሙሉ አቅም እንዳላቸው የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
Next article“ሱዳን በድንበር አካባቢ የምታደርገውን ሕገወጥ እንቅስቃሴ ቀጥላለች” የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር