ከ290 ሽህ ዶላር በላይ የህክምና ቁሳቁስ ተበረከተ፡፡

123
ከ290 ሽህ ዶላር በላይ የህክምና ቁሳቁስ ተበረከተ፡፡
ባሕር ዳር፡ ጥር 03/2013 ዓ.ም (አብመድ) በአሜሪካ የሚገኝ ምህረት የህክምና ቁሳቁስ አቅራቢ የተባለ ድርጅት 290 ሽህ 281 ዶላር የሚያወጡ የመድኃኒት እና የግል ጤና መጠበቂያ መሳሪያዎችን እንዳበረከተ በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍጹም አረጋ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡
የህክምና ቁሳቁሶቹ በኢትዮጵያ ለታካሚዎችና ለጤና ባለሙያዎች አገልግሎት ላይ እንደሚውሉ አምባሳደሩ ገልፀዋል፡፡
አምባሳደሩ ለተበረከተው የህክምና ቁሳቁስ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአብመድ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
በዌብሳይት www.amharaweb.com
በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ
Previous articleየህጻናትን ፍልሰት ለመከላከል ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል፡፡
Next articleአማራ ክልል 3 ሚሊዮን ገደማ ለሚሆኑ ዜጎች የዕለት ደራሽ ምግብ እያቀረበ መሆኑን የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ፕሮግራም እና ልዩ ድጋፍ የሚሹ አካባቢዎች ማስተባበሪያ ኮሚሽን አስታወቀ።