15ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል አገር አቀፍ ሲምፖዚየም መርሐግብር እየተካሄደ ነው፡፡

720

ባሕር ዳር፡ ኅዳር 29/2013 ዓ.ም (አብመድ) 15ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፤ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል አገር አቀፍ ሲምፖዚየም መርሐግብር በአዲስ አበባ በመካሔድ ላይ ይገኛል።

በመርሐግብሩ ላይ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አደም ፋራህ፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ ሚኒስትሮችና የብሔር ብሔረሰብ ተወካዮች እና የሐይማኖት መሪዎች መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

መርሐግብሩ በወራሪው፣ ተስፋፊውና አሸባሪው ትህነግ ቡድን ክህደት ተፈፅሞባቸው ለተሰው የሰራዊት አባላት የህሊና ጸሎት ተደርጎ ተጀምሯል።

Previous article“ባለፉት 27 ዓመታት በንግዱ ዘርፍ እኩል የሆነ የተሳትፎ ዕድል አልነበረም ” አቶ ክቡር ገና የአፍሪካ ንግድ ምክር ቤት ሥራ አስኪያጅ
Next article“እኩይ ተልዕኮ ተሸክሞ ሲንቀሳቀስ የነበረው የህወሓት ቡድን ተወግዶ መከበሩ ቀኑን ልዩ ያደርገዋል” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን