ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ያስወነጨፈቻትን ˝ኢት አር ኤስ ኤስ 1˝ ሳታላይት በይፋ ከቻይና ተረከበች፡፡

506
ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ያስወነጨፈቻትን ˝ኢት አር ኤስ ኤስ 1˝ ሳታላይት በይፋ ከቻይና ተረከበች፡፡
ባሕር ዳር፡ ኅዳር 23/ 2013ዓ.ም (አብመድ) ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ከቻይናው ታዩዋን ከተማ የሳተላይት ማስወንጨፊያ ማዕከል ወደ ህዋ ያስወነጨፈቻትን ˝ኢት አር ኤስ ኤስ 1˝ በይፋ ከቻይና ተረክባለች።
የሳተላይቷ ይፋዊ ርክክብ ቀደም ብሎ በሁለቱ ሀገራት የዘርፉ መስሪያ ቤቶች በኩል ለማከናወን ሲጠበቅ የነበረ ቢሆንም የኮሮና ቫይረስ በፈጠረው የጉዞ መስተጓጎል ምክንያት ሳይከናወን መቆየቱ ተጠቁሟል።
በዚህም በሁለቱ ወገን በተደረሰ ስምምነት በቻይና ኢትዮጵያ አምባሳደር ተሾመ ቶጋ እንዲረከቡ በተወሰነው መሰረት በቻይና ስፔስ ቴክኖሎጂ አካዳሚ በተካሄደ ስነ-ስርዓት ርክክቡ መፈፀሙን ፋብኮ ዘግቧል፡፡
ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ታህሳስ 10 ቀን 2012 ዓ.ም ሳይተላይቷን ማስወንጨፏ የሚታወስ ነው።
Previous articleበቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዛሬም በንጹሃን ዜጎች ላይ ጥቃት መፈጸሙን ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡
Next articleበአማራ ክልል የሚገኙ ከተሞች በከተማ አስተዳደርነት እንዲመሩ መወሰኑ ለከተሞቹ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ዕድገት መፋጠን አስተዋጾ እንዳለው የሞላሌ እና የሻሁራ ከተማ የሥራ ኃላፊዎች ተናገሩ፡፡